Telegram Group & Telegram Channel
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (17)

13. ንግግርህ ብቁ ይሁን (ለ)

1. አዳምጥ

ጥሩ ተናጋሪ ጥሩ አድማጭ ፣ ጥሩ ፀሐፊ ጥሩ አንባቢ ነው ። ሰውዬው ራሱን በልቶት እግሩን ብታክለት ከማስደሰት ይልቅ ታሳምመዋለህ ። ሳያዳምጡ መናገርም እንዲሁ ነው ። ማዳመጥ ሰዎችን ለመረዳትና ለመርዳት ጥልቅ ፍላጎት ማሳየት ነው ። ያልተረዳኸውን ሰው መርዳት አትችልም ። ሰዎች ከእርዳታ ይልቅ አሳባቸውን የሚረዳላቸው/የሚያውቅላቸው ሰው ይፈልጋሉ ። ብዙ ሰው ከአእምሮ ሕመሙ የሚድነው ስታዳምጠው ነው ። አዳምጠህ ስትናገር ርእስ ትጠብቃለህ ፣ ያንን ሰው ትማርከዋለህ ። ደግሞም የመጨረሻው ይጸናልና ኋላ መናገር መልካም ነው ።

2. ንግግር አታቋርጥ

ሰው አሳቡን መጨረስ አለበት ። ምንም ቢናገር ዓመት አያወራም ። ስለዚህ ንግግሩን አስጨርሰው ። አሳቡ እንዳይጠፋህ ማስታወሻ ያዝ ። የሰው ልጅ አስተማማኝ ሰላም እንዳለው ምልክቱ ታግሦ መስማት ሲችል ነው ። ለአንድ ሰዓት ስብከት የሚሰሙ ሰዎች አንድ ነገር አላቸው ። እርሱም የውስጥ ሰላም ነው ። እግዚአብሔርን የሚያህል ትልቅ አምላክ የሚሰማው ነውና ሰውን ለማዳመጥ አትፈተን ። የተጨነቁ ሰዎች ትልቁ ችግራቸው የሚሰማቸው ሰው ማጣት ነው ። በትክክል እንደ ሰማሃቸው ካወቁ ምንም ምክር ሳትሰጣቸው ይፈወሳሉ ። ማዳመጥም አገልግሎት ነው ። ጆሮውን ላልነፈገን ጌታ ውለታው የተጨነቁትን መስማት ነው ።

3. በአሉታዊ ንግግር አትጀምር

ሰዎችን ከጉድለታቸው ተነሥተህ ስታወራቸው ዋጋ የላችሁም እያልካቸው ይመስላቸዋል ። ዋጋ የለህም ያልከው ዋጋህን ያሳጣሃል ። እግዚአብሔር ሲናገር ሁልጊዜ ከመልካሙ ጀምሮ ነው ። ሙሴን አንተ ገዳይ አላለውም ፣ ነጻ አውጪ አለው ። ጌዴዎን የፈሪዎች ሊቀ መንበር ቢሆንም አንተ ጎበዝ አለው ። የሞተውን የናይን መበለት ልጅ አንተ ሬሳ ሳይሆን “አንተ ጎበዝ” አለው ። ሬሳን “አንተ ጎበዝ” የሚል የእኔ መድኃኔ ዓለም ብቻ ነው ። ለሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት መልእክት ሲላክ ካላቸው ጥሩ ነገር ተነሥቶ የሌላቸውን ይናገራቸዋል (ዘጸ. 3 ፡ 10 ፤ መሳ. 6 ፡ 12 ፤ ሉቃ. 7 ፡ 14 ፤ ራእ. 2 ፡ 2-7) ። በንግግር መነሻ ላይ ከጉድለት መጀመር ግንኙነትን በዜሮ ማባዛት ነው ። ሰዎች የሚጠሉት ዋጋ የላችሁም የሚል ድምፅን ነው ። የምትነቅፋቸው ሊያጠፉህ ይችላሉና ተጠንቀቅ ። ከትዳር አጋር ጋር የማትግባቡት ከጉድለት ስለምትጀምሩ ነው ። ሰይጣን በወኪል ሳይሆን በቀጥታ የሚዋጋህ “ዋጋ የለህም” በሚል ድምፅ ነው ። ሰው ራሱን የሚያጠፋው የራሱ ዋጋ ሲወርድበት ነው ። “ብኖርም ብሞትም የምጠቅምና የማጎዳ ሰው አይደለሁም” ሲል በራሱ ላይ ይጨክናል ።
ይቀጥላል

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 22 ቀን 2016 ዓ.ም.



tg-me.com/Nolawii/3926
Create:
Last Update:

የሕይወት ሥነ ሥርዓት (17)

13. ንግግርህ ብቁ ይሁን (ለ)

1. አዳምጥ

ጥሩ ተናጋሪ ጥሩ አድማጭ ፣ ጥሩ ፀሐፊ ጥሩ አንባቢ ነው ። ሰውዬው ራሱን በልቶት እግሩን ብታክለት ከማስደሰት ይልቅ ታሳምመዋለህ ። ሳያዳምጡ መናገርም እንዲሁ ነው ። ማዳመጥ ሰዎችን ለመረዳትና ለመርዳት ጥልቅ ፍላጎት ማሳየት ነው ። ያልተረዳኸውን ሰው መርዳት አትችልም ። ሰዎች ከእርዳታ ይልቅ አሳባቸውን የሚረዳላቸው/የሚያውቅላቸው ሰው ይፈልጋሉ ። ብዙ ሰው ከአእምሮ ሕመሙ የሚድነው ስታዳምጠው ነው ። አዳምጠህ ስትናገር ርእስ ትጠብቃለህ ፣ ያንን ሰው ትማርከዋለህ ። ደግሞም የመጨረሻው ይጸናልና ኋላ መናገር መልካም ነው ።

2. ንግግር አታቋርጥ

ሰው አሳቡን መጨረስ አለበት ። ምንም ቢናገር ዓመት አያወራም ። ስለዚህ ንግግሩን አስጨርሰው ። አሳቡ እንዳይጠፋህ ማስታወሻ ያዝ ። የሰው ልጅ አስተማማኝ ሰላም እንዳለው ምልክቱ ታግሦ መስማት ሲችል ነው ። ለአንድ ሰዓት ስብከት የሚሰሙ ሰዎች አንድ ነገር አላቸው ። እርሱም የውስጥ ሰላም ነው ። እግዚአብሔርን የሚያህል ትልቅ አምላክ የሚሰማው ነውና ሰውን ለማዳመጥ አትፈተን ። የተጨነቁ ሰዎች ትልቁ ችግራቸው የሚሰማቸው ሰው ማጣት ነው ። በትክክል እንደ ሰማሃቸው ካወቁ ምንም ምክር ሳትሰጣቸው ይፈወሳሉ ። ማዳመጥም አገልግሎት ነው ። ጆሮውን ላልነፈገን ጌታ ውለታው የተጨነቁትን መስማት ነው ።

3. በአሉታዊ ንግግር አትጀምር

ሰዎችን ከጉድለታቸው ተነሥተህ ስታወራቸው ዋጋ የላችሁም እያልካቸው ይመስላቸዋል ። ዋጋ የለህም ያልከው ዋጋህን ያሳጣሃል ። እግዚአብሔር ሲናገር ሁልጊዜ ከመልካሙ ጀምሮ ነው ። ሙሴን አንተ ገዳይ አላለውም ፣ ነጻ አውጪ አለው ። ጌዴዎን የፈሪዎች ሊቀ መንበር ቢሆንም አንተ ጎበዝ አለው ። የሞተውን የናይን መበለት ልጅ አንተ ሬሳ ሳይሆን “አንተ ጎበዝ” አለው ። ሬሳን “አንተ ጎበዝ” የሚል የእኔ መድኃኔ ዓለም ብቻ ነው ። ለሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት መልእክት ሲላክ ካላቸው ጥሩ ነገር ተነሥቶ የሌላቸውን ይናገራቸዋል (ዘጸ. 3 ፡ 10 ፤ መሳ. 6 ፡ 12 ፤ ሉቃ. 7 ፡ 14 ፤ ራእ. 2 ፡ 2-7) ። በንግግር መነሻ ላይ ከጉድለት መጀመር ግንኙነትን በዜሮ ማባዛት ነው ። ሰዎች የሚጠሉት ዋጋ የላችሁም የሚል ድምፅን ነው ። የምትነቅፋቸው ሊያጠፉህ ይችላሉና ተጠንቀቅ ። ከትዳር አጋር ጋር የማትግባቡት ከጉድለት ስለምትጀምሩ ነው ። ሰይጣን በወኪል ሳይሆን በቀጥታ የሚዋጋህ “ዋጋ የለህም” በሚል ድምፅ ነው ። ሰው ራሱን የሚያጠፋው የራሱ ዋጋ ሲወርድበት ነው ። “ብኖርም ብሞትም የምጠቅምና የማጎዳ ሰው አይደለሁም” ሲል በራሱ ላይ ይጨክናል ።
ይቀጥላል

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 22 ቀን 2016 ዓ.ም.

BY Nolawi ኖላዊ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/Nolawii/3926

View MORE
Open in Telegram


Nolawi ኖላዊ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Spiking bond yields driving sharp losses in tech stocks

A spike in interest rates since the start of the year has accelerated a rotation out of high-growth technology stocks and into value stocks poised to benefit from a reopening of the economy. The Nasdaq has fallen more than 10% over the past month as the Dow has soared to record highs, with a spike in the 10-year US Treasury yield acting as the main catalyst. It recently surged to a cycle high of more than 1.60% after starting the year below 1%. But according to Jim Paulsen, the Leuthold Group's chief investment strategist, rising interest rates do not represent a long-term threat to the stock market. Paulsen expects the 10-year yield to cross 2% by the end of the year. A spike in interest rates and its impact on the stock market depends on the economic backdrop, according to Paulsen. Rising interest rates amid a strengthening economy "may prove no challenge at all for stocks," Paulsen said.

Nolawi ኖላዊ from id


Telegram Nolawi ኖላዊ
FROM USA